በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

የሽፋኑ ርዕሰ ጉዳይ | መጽሐፍ ቅዱስ በዛሬው ጊዜ ይጠቅማል?

ራስን መግዛት

ራስን መግዛት

የመጽሐፍ ቅዱስ መመሪያ፦ “ተላላ ሰው ቍጣውን ያለ ገደብ ይለቀዋል፤ ጠቢብ ሰው ግን ራሱን ይቈጣጠራል።”ምሳሌ 29:11

“ከሞት የተነሳሁ ያህል ሆኖ ይሰማኛል!”

የሚያስገኘው ጥቅም፦ ራስን መግዛት የሚያስገኛቸውን ጥቅሞች ዘርዝረን መጨረስ አንችልም! ለአብነት ያህል፣ ለጤንነታችን የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ማንሳት ይቻላል። መጽሐፍ ቅዱስ “የሰከነ ልብ ለሰውነት ሕይወት ይሰጣል” በማለት ይናገራል። በተጨማሪም “ደስተኛ ልብ ጥሩ መድኅኒት ነው” ይላል። (ምሳሌ 14:30 NW፤ 17:22) በአንጻሩ ደግሞ ጠበኛና ግልፍተኛ የሆኑ ሰዎች በተለያዩ በሽታዎች በተለይ ከልብ ጋር በተያያዙ ሕመሞች የመጠቃት አጋጣሚያቸው ከፍተኛ እንደሆነ ጥናቶች ያሳያሉ። እርግጥ ነው፣ ራስን መግዛት የሚጠቅመው ለጤንነታችን ብቻ አይደለም።

ካስያስ በአሁኑ ጊዜ በ30ዎቹ ዕድሜ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን እንዲህ ብሏል፦ “ጠበኛና ግልፍተኛ የነበርኩ ከመሆኑም ሌላ ብዙ ጊዜ ከሰዎች ጋር ለመጣላት ነገር እፈላልግ ነበር። ለራሴ አክብሮት አልነበረኝም። የመጽሐፍ ቅዱስን መመሪያዎች ሥራ ላይ ማዋል ስጀምር ግን ይህ ሁሉ ተለወጠ። ቁጣዬን መቆጣጠር እንዲሁም ትሑትና ይቅር ባይ መሆን ቻልኩ። እንዲህ ባላደርግ ኖሮ ዛሬ የምገኘው እስር ቤት ነበር። በእርግጥም ከሞት የተነሳሁ ያህል ሆኖ ይሰማኛል!”

ካስያስ ቁጣውን መቆጣጠርና ይቅር ባይ መሆን ችሏል