በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

የሽፋኑ ርዕሰ ጉዳይ | የይሖዋ ምሥክሮች እነማን ናቸው?

የስብከቱ ሥራ ወጪ የሚሸፈነው እንዴት ነው?

የስብከቱ ሥራ ወጪ የሚሸፈነው እንዴት ነው?

በየዓመቱ በብዙ መቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መጽሐፍ ቅዱሶችንና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጽሑፎችን አትመን እናሠራጫለን። በዓለም ዙሪያ ቅርንጫፍ ቢሮዎችንና የማተሚያ ሕንፃዎችን የምንገነባ ከመሆኑም ሌላ በእነዚህ ቦታዎች ላይ ሰፊ ሥራ እናከናውናለን። በአሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ጉባኤዎች የመንግሥት አዳራሽ ተብለው በሚጠሩ ባልተንቆጠቆጡ ሆኖም በሚያምሩ የአምልኮ ቦታዎች ውስጥ ይሰበሰባሉ። ታዲያ ይህ ሁሉ ወጪ የሚሸፈነው እንዴት ነው?

ሥራችን ሙሉ በሙሉ የሚካሄደው ሰዎች በፈቃደኝነት በሚሰጡት መዋጮ ነው። (2 ቆሮንቶስ 9:7) በ1879 የዚህ መጽሔት ሁለተኛ እትም የሚከተለውን ሐሳብ አስፍሮ ነበር፦ “‘የጽዮን መጠበቂያ ግንብ’ [በዚያን ጊዜ የመጽሔቱ ስም ይህ ነበር] ደጋፊ ይሖዋ ራሱ እንደሆነ እናምናለን። ይህ በመሆኑም መጠበቂያ ግንብ፣ ከሰዎች ድጋፍ ለማግኘት በፍጹም አይለምንም ወይም አይማጠንም።” አሁንም ቢሆን በዚህ ፖሊሲ ላይ ያደረግነው አንዳች ለውጥ የለም።

ግለሰቦች የገንዘብ መዋጮ በቀጥታ ወደ ቅርንጫፍ ቢሮዎቻችን ይልካሉ፤ አሊያም በመሰብሰቢያ አዳራሾቻችን በሚገኝ የመዋጮ ሣጥን ውስጥ ይከታሉ። ይሁን እንጂ አሥራት አናስከፍልም፣ ሙዳየ ምፅዋት አናዞርም ወይም ለምናከናውነው አገልግሎትም ሆነ ለጽሑፎቻችን ገንዘብ አንጠይቅም። በስብከቱ ሥራ ስንካፈል፣ በጉባኤ ውስጥ ስናስተምር ወይም የአምልኮ ቦታዎችን ለመገንባቱ ሥራ እገዛ ስናበረክት ገንዘብ አይከፈለንም። ኢየሱስም ቢሆን “በነፃ እንደተቀበላችሁ በነፃ ስጡ” ብሏል። (ማቴዎስ 10:8) በቅርንጫፍ ቢሮዎቻችን እንዲሁም የይሖዋ ምሥክሮች የበላይ አካል አባላትን ጨምሮ በዋናው መሥሪያ ቤታችን ያሉት የሃይማኖታዊ ማኅበሩ አባላት በሙሉ ደሞዝ አይከፈላቸውም።

“የይሖዋ ምሥክሮች በሚያደርጓቸው ሌሎች እንቅስቃሴዎችም ላይ ማየት እንደሚቻለው አንድ ሰው ለሃይማኖቱ ‘መዋጮ’ የሚሰጠው በራሱ ፈቃድ ሲሆን የመዋጮውን መጠንም ሆነ የሚሰጥበትን ጊዜ የሚወስነው ግለሰቡ ራሱ ነው።”—የአውሮፓ የሰብዓዊ መብቶች ፍርድ ቤት፣ 2011

በተጨማሪም በመዋጮ የተገኘው ገንዘብ አደጋ በደረሰባቸው አካባቢዎች እርዳታ ለመስጠት ይውላል። የጥንቶቹ ክርስቲያኖች መከራ ለደረሰባቸው ወንድሞቻቸው የበኩላቸውን እርዳታ ማበርከት በመቻላቸው ደስተኞች ነበሩ። (ሮም 15:26) እኛም በአደጋ ለተጎዱ የእምነት ባልንጀሮቻችን መኖሪያ ቤታቸውንና የአምልኮ ቦታቸውን መልሰን በመገንባት እንዲሁም ምግብ፣ ልብስና ሕክምና በመስጠት እርዳታ እናበረክታለን።