ለይሖዋ ዘምሩ—አዲስ መዝሙሮች

ይሖዋን ለማወደስና ለማምለክ የምንጠቀምባቸውን አዳዲስ መዝሙሮች አዳምጥ። ሙዚቃውንና ግጥሞቹን ካወረድክ በኋላ እነዚህን ግሩም መዝሙሮች ተለማመዳቸው።

መዝሙር 136

በሰማይ የተቋቋመው መንግሥት ይምጣልን!

ይህ ግሩም መዝሙር፣ በክርስቶስ ኢየሱስ የሚመራውን የአምላክ መንግሥት በማቋቋሙ ይሖዋ አምላክን ለማመስገን የተዘጋጀ የውዳሴ መዝሙር ነው።

መዝሙር 137

ድፍረት ስጠን

ይሖዋ ስለ ስሙ ስንመሠክር ድፍረት እንዲሰጠን የምናቀርበውን ልመና የያዘውን ይህን መዝሙር እንድትዘምር እንጋብዝሃለን።

መዝሙር 138

ስምህ ይሖዋ ነው

የይሖዋን ክቡር ስም አወድሱ፤ እንዲሁም እሱ ሉዓላዊ አምላክ መሆኑን ለሰዎች ሁሉ ንገሩ።

መዝሙር 139

ጸንተው እንዲቆሙ አስተምሯቸው

ይሖዋ አምላክ ጥበቃ እንዲያደርግልን እንዲሁም የሕይወትን ሩጫ በጽናት ለመጨረስ እንዲረዳን የቀረበ ልመና።

መዝሙር 140

የአቅኚ ሕይወት

ለይሖዋ ያለህን ፍቅር እንዲሁም እሱ ስለሰጠህ የሚያረካ ሥራና አስደሳች ሕይወት የሚሰማህን ስሜት በመዝሙር ግለጽ።

መዝሙር 141

ሰላም ወዳዶችን መፈለግ

ለሰዎች ፍቅር እንዳለን ብሎም የአምላክን ውድ በጎች ለማግኘት ትጋት የተሞላበት ፍለጋ እንደምናደርግ የሚገልጽ አስደሳች መዝሙር።

መዝሙር 142

ለሁሉም ዓይነት ሰዎች መስበክ

ስለ ይሖዋ ጥሩነት ዘምር፤ እንዲሁም ሁሉም ዓይነት ሰዎች የእሱ ወዳጆች እንዲሆኑ የመርዳት መብት በማግኘትህ የሚሰማህን አድናቆት በመዝሙር ግለጽ።

መዝሙር 143

በጨለማ ዓለም ውስጥ ብርሃን ማብራት

የምንሰብከው መልእክት ብሩህ ነው፤ በጨለማ ያበራል።

መዝሙር 144

ስብከታችን ሰው ያድናል

ጊዜው ከማለቁ በፊት የአምላክን መልእክት ለሰዎች መስበክ አለብን።

መዝሙር 145

ለአገልግሎት መዘጋጀት

ከሞቀ አልጋ ወጥቶ በቅዝቃዜ ማገልገል ከባድ ቢሆንም በዚህ ሁኔታ ለመስበክ ምን ማበረታቻ ማግኘት ይቻላል?

መዝሙር 146

ለእኔ እንዳደረጋችሁት ይቆጠራል

ኢየሱስ፣ ለተቀቡ ወንድሞቹ የሚደረገውን ማንኛውም እርዳታና ድጋፍ ለእሱ እንደተደረገ ይቆጥረዋል።

መዝሙር 147

ልዩ ንብረት

ይሖዋ፣ በመንፈስ የተቀቡ ልጆቹን ይወዳቸዋል፤ እነሱም የእሱን ፈቃድ ማድረግ ያስደስታቸዋል።

መዝሙር 148

አንድያ ልጅህን ሰጠኸን

እጅግ ውድ የሆነ ስጦታ ስለሰጠን ይሖዋ ይመስገን። ይህ ስጦታ ሁላችንም ተስፋ እንዲኖረን አድርጓል።

መዝሙር 149

ለቤዛው አመስጋኝ መሆን

ኢየሱስ በፈቃደኝነት ለእኛ ሲል ሕይወቱን አሳልፎ መስጠቱ እስከ ዛሬ ከታዩት የፍቅር መግለጫዎች ሁሉ እጅግ የላቀ ነው እንድንል ያደርገናል፤ ይህ ስጦታ ይሖዋን ለዘላለም እንድናመሰግን ይገፋፋናል።

መዝሙር 150

እገዛ የሚያስፈልጋቸውን መርዳት

ይሖዋን እሱ በሚፈልገው በማንኛውም መንገድ ማገልገል እንደሚያስደስትህ በመዝሙር ግለጽ።

መዝሙር 151

የአምላክ ልጆች መገለጥ

ይሖዋ፣ የክርስቶስ ወንድሞችን ወደ ሰማይ የሚወስድበትንና ከክርስቶስ ጋር ድል የሚያደርጉበትን እንዲሁም አብረውት የሚነግሱበትን ጊዜ በጉጉት እንጠባበቃለን።

መዝሙር 152

ኃይላችን፣ ተስፋችን፣ ትምክህታችን

የሕይወት ውጣ ውረድ ሲከብደን አምላክ ኃይላችን፣ ተስፋችንና ትምክህታችን ነው።

መዝሙር 153

ምን ይሰማሃል?

ቅኖችን ለመፈለግ የምትችለውን ሁሉ በማድረግህ ምን ተሰማህ?

መዝሙር 154

ጸንተን እንጠብቃለን

በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥም ይሖዋን በታማኝነት እስከ መጨረሻው ማገልገላችንን እንድንቀጥል የሚረዳ መዝሙር።