በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

የይሖዋ ምሥክሮች ከቤት ወደ ቤት የሚሄዱት ለምንድን ነው?

የይሖዋ ምሥክሮች ከቤት ወደ ቤት የሚሄዱት ለምንድን ነው?

 ኢየሱስ ‘ከሁሉም ብሔራት ሰዎችን ደቀ መዛሙርት እንዲያደርጉ’ ለተከታዮቹ ነግሯቸው ነበር። (ማቴዎስ 28:19, 20) ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን ለስብከት ሲልካቸው ሰዎችን በየቤታቸው እየሄዱ እንዲያናግሩ መመሪያ ሰጥቷቸው ነበር። (ማቴዎስ 10:7, 11-13) ኢየሱስ ከሞተ በኋላም በመጀመሪያው መቶ ዘመን ይኖሩ የነበሩት ክርስቲያኖች “በአደባባይና ከቤት ወደ ቤት” በመሄድ መልእክታቸውን ማሰራጨታቸውን ቀጥለው ነበር። (የሐዋርያት ሥራ 5:42፤ 20:20) እኛም የጥንቶቹን ክርስቲያኖች አርዓያ እንከተላለን፤ ደግሞም ከቤት ወደ ቤት ማገልገል ሰዎችን ለማግኘት የተሻለ መንገድ እንደሆነ ይሰማናል።